በኢትዮጵያ የሚገኙ የቤት ሠራተኞችን የሙያ ስልጠና በመስጠትና የብቃት ምዘና ፈተና (COC) እንዲወስዱ ለማድረግ እየተሰራበት እንደሚገኝ ተገለጸ

Date:

የቤት ውስጥ ሠራተኞች ራሳቸውን በሙያ ብቁ የሚያደርጉበት ስልጠና በመስጠትና የሙያ ብቃታቸውን የሚመዝን ፈተና (COC) እንዲወስዱ ለማድረግ እየተሰራበት እንደሚገኝ አንድነት ኢትዮጵያ የቤት ውስጥ ሠራተኞች ማኅበራት ሕብረት አስታውቋል፡፡

የቤት ሠራተኞች በማኅበር ከመደራጀት በዘለለ ስልታዊ የሆነ የሙያ ክህሎታቸውንና ደረጃቸውን ሊመዝኑ የሚችሉ ተቋማቶች በሀገር አቀፍ ደረጃ መኖራቸውን የሕብረቱ ፕሬዝዳንት ሂሩት አበራ ገልጸዋል።

በመሆኑም በሥራና ክህሎት በኩል ተግባራዊ በሚደረገው አሰራር መሠረት ማንኛውም ሰው መሠረታዊ የሆኑ ምዘናዎችን በመውሰድ ራሱን ብቁ ማድረግ የሚችልበት አግባብ በመኖሩ፤ የቤት ሠራተኞችም የትምህርት ደረጃቸው ሳይፈለግ በሙያቸው ብቻ ብቁ መሆናቸውን የሚያረጋግጡበት ምዘና ስለመኖሩ አስታውቀዋል።

በዚህም መሠረት ለሙያው ብቁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የብቃት ምዘና (COC) እንዲወስዱ ለማድረግ ማኅበሩ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

“ከዚህ ጎን ለጎንም ራሳቸውን አብቅተውና የመደራደር አቅማቸውን ጨምረው ከአሠሪዎቻቸው ጋር የሚችሉትን ሙያ በማሳየት ብቁ ከሆኑ በሙያቸውና በምዘናቸው መሠረት የሚቀጠሩበትን መንገድ ለማመቻቸትም እየተሰራበት ይገኛል” ብለዋል።

የሙያ ብቃት ምዘናውን (COC) ማንኛውም ‘በሙያዬ ብቁ ነኝ’ ያለ ሰው ምዘናው በሚሰጥበት ተቋም ውስጥ መፈተን የሚችል ሲሆን ስልጠና የሚያስፈልጋቸው ደግሞ ከአንድ ወር ከግማሽ እስከ 6 ወር በሚደርሱ አጫጭር ስልጠናዎች መሰረት ራሳቸውን ማብቃት እንደሚችሉ ተናግረዋል።

ከዚህ ባሻገርም በኢትዮጵያ ለቤት ሠራተኞች ትምህርትና ስልጠና እንዲሁም ሙሉ ጊዜ ገብተው መሰልጠን የሚፈልጉ የቤት ሠራተኞችን በተመለከተም በዛ ልክ የተዘጋጀ ፖሊሲ ባለመኖሩ ስርዓተ ትምህርቱ ላይ ማስተካከያዎች እንዲደረጉ ከትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋራ እየተሰራበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...