በእስራኤል ባለፉት 24 ሰዓታት 191 ሰዎች ቆሰሉ

Date:

የእስራኤል የጤና ሚኒስቴር ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በነበረው ውጥረት 191 እስራኤላውያን ቆስለው ወደ ሆስፒታሎች መግባታቸውን ይፋ አድርጓል።

ከተጎዱት መካከል ወታደሮችና ሲቪሎች የሚገኙበት ሲሆን፣ የአንዳንዶቹ ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑ ተገልጿል። ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ አንስቶ እስካሁን 2,339 ሰዎች የሕክምና ዕርዳታ ማግኘታቸውን ዘ ታይምስ ኦፍ እስራኤል ዘግቧል።

በሌላ በኩል፣ ግጭቱ እየተባባሰ መምጣቱን ተከትሎ በቤሩት የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በሊባኖስ ለሚገኙ ዜጎቹ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።

ዜጎቹ የምግብ፣ የውሃና የመድኃኒት አቅርቦት በማዘጋጀት አስተማማኝ መጠለያ ውስጥ እንዲቆዩ አሳስቧል።

በሊባኖስ በኩል ደግሞ በእስራኤልና በሂዝቦላ መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውንና የሟቾች ቁጥር ቢያንስ 486 መድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...