በወንጀል ድርጊት ስለሚገኘ ንብረትን ጉባዔ እየተካሄደ ነው

Date:


የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ/ ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መከላከል ቡድን 50ኛ የከፍተኛ ሃላፊዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡


በጉባዔው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሐይ ጳውሎስ፣ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሙሉቀን አማረ እና የቡድኑ ሊቀ መንበር ፍሬዘር አያሌው ተገኝተዋል፡፡


የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መከላከል ቡድን ዓመታዊ ጉባዔ ከነሐሴ 16 እስከ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።


በዛሬው ዕለት የተጀመረው የቡድኑ ከፍተኛ ሃላፊዎች ጉባዔም የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መከላከል ቡድን ዓመታዊ ጉባዔ አካል ነው፡፡


በጉባዔው ከአባል ሀገራቱ፣ ከአንድ ታዛቢ ሀገር እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወጣጡ 1 ሺህ 150 በላይ ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡


ኢትዮጵያ በቀጣናው በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መከላከል ላይ በንቃት እየተሳተፈች እንደምትገኝ በመድረኩ ተነስቷል፡፡


በዘርፉ የሕግ ማሻሻያ ከማድረግ ጀምሮ ከተለያዩ ሀገራት ጋር በትብብርና በቅንጅት እየሰራች መሆኑም ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...