በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ስብሰባ ሊካሄድ ነው

Date:

በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ጦር ጉዳይ ከ20 በላይ ሀገራት የሚሳተፉበት ከፍተኛ ወታደራዊ ስብሰባ ዛሬ በብሪታንያ ይካሄዳል ተብሏል፡፡

በስብሰባው ላይ ብሪታንያና ፈረንሳይ በሚመሩት የሰላም ማስከበር ተልዕኮው ጥምረት የተካተቱ ሀገራት ከፍተኛ ወታደራዊ መሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን÷ በዕቅዱ አተገባበር ዙሪያ በዝግ ይመክራሉ ተብሏል፡፡

በስብሰባው ላይ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃልኪዳን ድርጅት (ኔቶ) እና የአውሮፓ ህብረት እንደሚሳተፉም ተገልጿል፡፡

በምዕራባውያኑ ሀገራት የሚመራው በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ወታደሮችን የማሰማራት ዕቅድ ወደ ትግበራ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኬር ስታርመር ተናግረዋል፡፡

ፈረንሳይ እና ብሪታንያ ወታደሮቻቸውን ወደ ዩክሬን ለመላክ ፍቃደኛ መሆናቸውንና ሌሎች የጥምረቱ ሀገራት በተለያዩ መንገዶች ድጋፍ እንደሚያደርጉ መግለጻቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...