በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ስብሰባ ሊካሄድ ነው

Date:

በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ጦር ጉዳይ ከ20 በላይ ሀገራት የሚሳተፉበት ከፍተኛ ወታደራዊ ስብሰባ ዛሬ በብሪታንያ ይካሄዳል ተብሏል፡፡

በስብሰባው ላይ ብሪታንያና ፈረንሳይ በሚመሩት የሰላም ማስከበር ተልዕኮው ጥምረት የተካተቱ ሀገራት ከፍተኛ ወታደራዊ መሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን÷ በዕቅዱ አተገባበር ዙሪያ በዝግ ይመክራሉ ተብሏል፡፡

በስብሰባው ላይ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃልኪዳን ድርጅት (ኔቶ) እና የአውሮፓ ህብረት እንደሚሳተፉም ተገልጿል፡፡

በምዕራባውያኑ ሀገራት የሚመራው በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ወታደሮችን የማሰማራት ዕቅድ ወደ ትግበራ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኬር ስታርመር ተናግረዋል፡፡

ፈረንሳይ እና ብሪታንያ ወታደሮቻቸውን ወደ ዩክሬን ለመላክ ፍቃደኛ መሆናቸውንና ሌሎች የጥምረቱ ሀገራት በተለያዩ መንገዶች ድጋፍ እንደሚያደርጉ መግለጻቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...