በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ስብሰባ ሊካሄድ ነው

Date:

በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ጦር ጉዳይ ከ20 በላይ ሀገራት የሚሳተፉበት ከፍተኛ ወታደራዊ ስብሰባ ዛሬ በብሪታንያ ይካሄዳል ተብሏል፡፡

በስብሰባው ላይ ብሪታንያና ፈረንሳይ በሚመሩት የሰላም ማስከበር ተልዕኮው ጥምረት የተካተቱ ሀገራት ከፍተኛ ወታደራዊ መሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን÷ በዕቅዱ አተገባበር ዙሪያ በዝግ ይመክራሉ ተብሏል፡፡

በስብሰባው ላይ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃልኪዳን ድርጅት (ኔቶ) እና የአውሮፓ ህብረት እንደሚሳተፉም ተገልጿል፡፡

በምዕራባውያኑ ሀገራት የሚመራው በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ወታደሮችን የማሰማራት ዕቅድ ወደ ትግበራ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኬር ስታርመር ተናግረዋል፡፡

ፈረንሳይ እና ብሪታንያ ወታደሮቻቸውን ወደ ዩክሬን ለመላክ ፍቃደኛ መሆናቸውንና ሌሎች የጥምረቱ ሀገራት በተለያዩ መንገዶች ድጋፍ እንደሚያደርጉ መግለጻቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...