ዩኒቨርሲቲው ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማስተማር የሚያስችለውን ስርዓተ ትምህርት አዘጋጅቷል ተብሏል።
ዩኒቨርሲቲው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በማድረግና ስርዓተ ትምህርት በመቅረፅ ዝግጅት ሲያደረግ መቆየቱን፥ ትምህርቱን ለመጀመር በተዘጋጀ የምክክር አውደ ጥናት ላይ ተገልጿል።
የግዕዝ ቋንቋ ትምህርት በሰርተፊኬት እና በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ከሚሰጡ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ይጠቀሳሉ።
