የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ የብሔራዊ የአልኮልና አረቄ ፋብሪካ ምርቶቹን ወደ ዓለም አቀፍ ገበያዎች በማስፋፋት ሽያጩን እንዲያሳድግ መክሯል።
የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እንዳስታወቀው፣ ፋብሪካው ዕድገቱን ማስቀጠል እንዲችል የግብይት ሥራዎችን ማጠናከር፣ ወደ ውጭ ገበያ መግባትና የሀገር ውስጥ የስርጭት መረቡን ማሻሻል ይኖርበታል ብሏል።
በተጨማሪም፣ የፋብሪካውን ምርታማነትና የማምረት አቅም በማሳደግ እንዲሁም ገቢ የሚያስገኙ ንብረቶችን በአግባቡ በመጠቀም ትልቅ ዋጋ መፍጠር እንደሚችል አስረድቷል።
ይህ የተባለው የፋብሪካው 2017 በጀት ዓመት አፈፃፀሙ በተገመገመበት ወቅት ነዉ። መንግስታዊዉ ኩባንያው በዓመቱ ከታክስ በፊት 340 ሚሊዮን ብር ትርፍ ያገኘ ሲሆን ሲደርስ፣ አጠቃላይ ገቢው ደግሞ 2.6 ቢሊዮን ብር መሆኑም ተመላክቷል።
CapitalNews
