በህንድ ሀገር መሰረቱን ያደረገው ቫይደም ሄልዝ በአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ቢሮውን ከፈተ
በውጭ ሀገራት ህክምና ለሚያስፈልጋቸው ህሙማን በማማከርና የጉዞ ሁኔታዎችን በማመቻቸት የሚታወቀውና በህንድ ሀገር መሰረቱን ያደረገው ቫይደም ሄልዝ በአዲስ አበባ ቅርንጫፉን በይፋ እንደከፈተ አስታውቋል።
“ቫይደም ሄልዝ አለም አቀፍ ልምዱን ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ ከህክምና ጉዞ ጋር ተያይዘው የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላትና ለታካሚዎችና ለቤተሰቦቻቸው እፎይታን ለመስጠት ያለመ” መሆኑን የቫይደም ሄልዝ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ሚስተር ፓንኬጅ ቻንድራ ተናግረዋል።
ቫይደም ሄልዝ በህንድ፣ ቱርክ፣ ታይላንድ፣ ዱባይ፣ ጀርመን፣ ቱኒዚያ፣ ግብፅ፣ ሲንጋፖር፣ ማሌዥያ እና ደቡብ ኮሪያ ከሚገኙ ከ 8,000 በላይ ዶክተሮች ጋር ግንኙነት ያለው ሲሆን እስካሁን ድረስም በዓለም ዙሪያ ከ 100,000 በላይ ታካሚዎች ህክምና እንዲያገኙ አስተዋጽኦ እንዳደረገም ተገልጿል።
ለተጨማሪው:https://t.me/E
