ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቲክቶክን በአሜሪካ ውስጥ ለተጨማሪ 75 ቀናት እንዲቆይ የሚያስችል የስራ አስፈፃሚ ትዕዛዝ መፈረማቸውን ማምሻውን አስታወቁ። ይህን ያደረጉት አስተዳደራቸው ቲክቶክ የአሜሪካ ንብረት እንዲሆን የሚያስችለውን ስምምነት ለመደራደር ተጨማሪ ጊዜ ለመስጠት እንደሆነ ተናግረዋል።
ትዕዛዙ ይፋ የሆነው የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት የመተግበሪያው ድርሻ በአብዛኛው ለአሜሪካ ባለሀብቶች ባለቤትነት ወደ ሚተዳደረው አዲስ የአሜሪካ ኩባንያ ለማሸጋገር ወደ ስምምነት እንደተቃረበ ፕሬዚዳንቱ በማመናቸው ነው።
የቻይናው ኩባንያ ባይትዳንስ ቲክቶክ ለአሜሪካ ባለሃብቶች ከተሸጠ በኋላ አናሳ ድርሻ እንደሚኖረው ጉዳዩን የሚያውቁ ምንጭ ተናግረዋል።
ሆኖም ትራምፕ ቻይናን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ሰፊ ታሪፎችን ካወጁ በኋላ ቤጂንግ ስምምነቱን ሐሙስ ማቋረጧ ተገልጿል። የባይትዳንስ ተወካዮች ወደ ዋይት ሀውስ በመደወል “ቻይና የንግድ እና የታሪፍ ድርድር እስከሚጀምር ድረስ የቲክቶክ ሽያጭ ስምምነቱን እንደማትቀበል ገልጸዋል” የሚሉት ምንጩ፣ ቻይናና አሜሪካ በዚህ ዙሪያ በሚቀጥሉት 75 ቀናት ውስጥ ይደራደራሉ ብለዋል።
