ቲክቶክ በአሜሪካ ውስጥ ለተጨማሪ 75 ቀናት እንደሚቆይ ተገለጸ

Date:

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቲክቶክን በአሜሪካ ውስጥ ለተጨማሪ 75 ቀናት እንዲቆይ የሚያስችል የስራ አስፈፃሚ ትዕዛዝ መፈረማቸውን ማምሻውን አስታወቁ። ይህን ያደረጉት አስተዳደራቸው ቲክቶክ የአሜሪካ ንብረት እንዲሆን የሚያስችለውን ስምምነት ለመደራደር ተጨማሪ ጊዜ ለመስጠት እንደሆነ ተናግረዋል።

ትዕዛዙ ይፋ የሆነው የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት የመተግበሪያው ድርሻ በአብዛኛው ለአሜሪካ ባለሀብቶች ባለቤትነት ወደ ሚተዳደረው አዲስ የአሜሪካ ኩባንያ ለማሸጋገር ወደ ስምምነት እንደተቃረበ ፕሬዚዳንቱ በማመናቸው ነው።

የቻይናው ኩባንያ ባይትዳንስ ቲክቶክ ለአሜሪካ ባለሃብቶች ከተሸጠ በኋላ አናሳ ድርሻ እንደሚኖረው ጉዳዩን የሚያውቁ ምንጭ ተናግረዋል።

ሆኖም ትራምፕ ቻይናን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ሰፊ ታሪፎችን ካወጁ በኋላ ቤጂንግ ስምምነቱን ሐሙስ ማቋረጧ ተገልጿል። የባይትዳንስ ተወካዮች ወደ ዋይት ሀውስ በመደወል “ቻይና የንግድ እና የታሪፍ ድርድር እስከሚጀምር ድረስ የቲክቶክ ሽያጭ ስምምነቱን እንደማትቀበል ገልጸዋል” የሚሉት ምንጩ፣ ቻይናና አሜሪካ በዚህ ዙሪያ በሚቀጥሉት 75 ቀናት ውስጥ ይደራደራሉ ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...