የ2018 አዲስ አመት ዋዜማ ኤግዚቢሽንን ለማዘጋጀት ዛሬ መጋቢት 16 ቀን በተከፈተው ጨረታ ታሜሶል ኮምኒኬሽን በ92 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር አሸናፊ ሆነ፡፡
በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማእከል የተዘጋጀውን የ2017 የአዲስ አመት ዋዜማ ያዘጋጀው ታሜሶል ቀጣዩን የአዲስ አመት ዋዜማ ለማስተናገድ ያቀረበው ዋጋ ከተከታዩ ተጫራች አንፃር የ6.9 ሚሊየን ብር ብልጫ አለው፡፡
በቀጣዮቹ ቀናት የሚከፈተውን የፋሲካ በዓል ዋዜማ ኤክስፖ ጨረታ በ60 ሚሊየን ብር አሸንፎ የሚያዘጋጀው ታሜሶል ኮምኒኬሽን አዳዲስ አቀራረቦችን በማስተዋወቅ የበዓል ዋዜማ ግብይቱ የተሻለ እና ሳቢ እንዲሆን እንደሚሰራ ነው ለካፒታል የገለጸው፡፡
