ትራምፕ ስለ ሆርሙዝ ወሽመጥ ያላቸውን ቅዠት በቅርቡ እናስተካክለዋለን

Date:

ዶናልድ ትራምፕ የሆርሙዝ ወሽመጥን “አዲስ የአሜሪካ ግዛት” ማለታቸውን ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ካዚም ጋሪባባዲ “ቅዠታም” ሲሉ ፕሬዝዳንቱን ወርፈዋል።

“ዶናልድ ትራምፕ የፐርዥያ ባሕረ ሰላጤን በትክክል መጻፍ እንደተማሩት ሁሉ ስለ ሆርሙዝ ወሽመጥ ያላቸውን ቅዠትም በቅርቡ እናስተካክለዋለን” ሲሉ ጽፈዋል።

ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ማኅበራዊ ሚዲያቸው በለጠፉት ምሥል ላይ የሆርሙዝ ወሽመጥን አክብበው “የአሜሪካ አዲስ ግዛት” ሲሉ ጽፈዋል።

የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትርም ይሄንን ምሥል በድጋሚ አጋርተዋል።

በሌላ በኩል የኢራን ፓርላማ አፈ ጉባዔ መሐመድ ባጋር ጋሊባፍ በበኩላቸው አሜሪካ የመግባቢያ ሰነዱን ስምምነቶች ካልተገበረች የሆርሙዝ ወሽመጥ እንደማይከፈት አስታውቀዋል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...

«ግብጽ ዛቻውን አቁማ ወደ ድርድር ትግባ!»

ታዋቂው የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝ ዶ/ር ዴቪድ ማትሳንጋ ግብጽ በኢትዮጵያ...