ትራምፕ ኢራን ያበለጸገችውን ዩራኒየም ለማስረከብ ተስማምታለች አሉ

Date:

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ያበለጸገችውን ዩራኒየም ለማስረከብ መስማማቷን ተናገሩ።

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል እየተካሄደ በነበረው የሰላም ድርድር ላይ ካላግባቡ ነጥቦች መካከል ቴህራን ያበለጸገችው ዩራኒየም አንዱ ነበር።

ፕሬዚዳንቱ በሳምንቱ መጨረሻ በዋሺንግተን እና በቴህራን መካከል ንግግር ሊቀጥል እንደሚችል ተናግረው፤ ከስምምነት ልንደርስ “በጣም ተቃርበናል” ብለዋል።

ትራምፕ በላስቬጋስ በአሜሪካ ምጣኔ ኃብት ላይ ባተኮረ ጉባዔ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ጦርነቱ “ያለምንም እንከን” እየሄደ እንደሆነ ተናግረው በቅርቡ ማብቃት አለበት ብለዋል።

ቀደም ሲል ዋይት ሐውስ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንደማይኖራት መስማማቷን ገልጾ ነበር።

አክሎም ባለፈው ዓመት እስራኤል እና አሜሪካ የፈጸሙትን ድብደባ ተከትሎ ከመሬት በታች እንደተቀበረ የሚታመነውን የበለጸገ ዩራኒየም “የኒውክሌር አቧራ” አራግፈው ቆፍረው እንደሚያወጡ ተናግረው ነበር።

ትራምፕ በቀጣይ ዙር በሚደረገው የሁለቱ አገራት ድርድር እርግጠኛ ሆነው ታይተዋል።

ነገር ግን ከአምስት ቀናት በኋላ የሚያበቃው የተኩስ አቁም ስምምነቱ ስለመራዘሙ እርግጠኛ አለመሆናቸውን ጨምረው ተናግረዋል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...