ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፈን ሀሰን በላውራ አዋርድ እጩ ሆና ቀረበች

Date:


በየአመቱ ስኬታማ ጊዜን ያሳለፉ ስፖርተኞች እውቅና የሚያገኙበት የላውራ አዋርድ በፓሪስ ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ያገኙ 6 አትሌቶች እጩ ሆነው ቀርበውበታል።

በሴቶች ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፈን ሀሰን ዕጩ ስትሆን አትሌቷ በፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን የወርቅ በ5ሺ እና በ10ሺ ደግሞ የነሀስ ሜዳልያ ማሳካቷም ይታወሳል።

በፓሪስ 2024 በ1500 ሜትር የወርቅና በ5ሺ ሜትር የብር ሜዳልያ ያገኝችው ኬንያዊቷ ፌዝ ኪፕየጎን አሜሪካዊቷ ማክ ላህሊን ሌቭሮን እና የሴንት ሉቺያዋ ጁሊያን አልፍሬዝ በሴቶች ዘርፍ በእጩነት የቀረቡ ሆነዋል።

በወንዶች ዘርፍ ደግሞ የምርኩዝ ዘላዩ ሙንዶ ዱፕላቲን እና የአጭር ርቀት ሯጩ የቦትስዋናው ሌትሲል ቴቦጎ ታጭተዋል።

በ7 ዘርፎች እውቅና በሚሰጥበት የላውራ ሽልማት ከአትሌቲክሱ ውጭ ሲሞን ባይልስ እና ካርሎስ አልካሬዝን ጨምሮ በርካቶች በእጩነት ተካተዋል።

ለ25ኛ ጊዜ በሚካሄደው ላውራ አዋርድ የመጨረሻው አሸናፊ ሚያዚያ 13 ቀን በማድሪድ የሚታወቅ ይሆናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...