ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፈን ሀሰን በላውራ አዋርድ እጩ ሆና ቀረበች

Date:


በየአመቱ ስኬታማ ጊዜን ያሳለፉ ስፖርተኞች እውቅና የሚያገኙበት የላውራ አዋርድ በፓሪስ ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ያገኙ 6 አትሌቶች እጩ ሆነው ቀርበውበታል።

በሴቶች ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፈን ሀሰን ዕጩ ስትሆን አትሌቷ በፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን የወርቅ በ5ሺ እና በ10ሺ ደግሞ የነሀስ ሜዳልያ ማሳካቷም ይታወሳል።

በፓሪስ 2024 በ1500 ሜትር የወርቅና በ5ሺ ሜትር የብር ሜዳልያ ያገኝችው ኬንያዊቷ ፌዝ ኪፕየጎን አሜሪካዊቷ ማክ ላህሊን ሌቭሮን እና የሴንት ሉቺያዋ ጁሊያን አልፍሬዝ በሴቶች ዘርፍ በእጩነት የቀረቡ ሆነዋል።

በወንዶች ዘርፍ ደግሞ የምርኩዝ ዘላዩ ሙንዶ ዱፕላቲን እና የአጭር ርቀት ሯጩ የቦትስዋናው ሌትሲል ቴቦጎ ታጭተዋል።

በ7 ዘርፎች እውቅና በሚሰጥበት የላውራ ሽልማት ከአትሌቲክሱ ውጭ ሲሞን ባይልስ እና ካርሎስ አልካሬዝን ጨምሮ በርካቶች በእጩነት ተካተዋል።

ለ25ኛ ጊዜ በሚካሄደው ላውራ አዋርድ የመጨረሻው አሸናፊ ሚያዚያ 13 ቀን በማድሪድ የሚታወቅ ይሆናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...