ቻይና የአለማችንን ፈጣንና ጭነት እራሱ የሚያራግፍ  ግዙፍ መርከብ ይፋ አደረገች

Date:

የቻይና የመርከብ ግንባታ ኮርፖሬሽን በጂያንግዙ ግዛት የጫነውን ጭነት በራሱ የሚያራግፍ የአለማችንን ፈጣኑን መርከብ በይፋ ስራ ማስጀመሩን ሲጂቲኤን ዘግቧል።

ይህ ግዙፍ መርከብ 215 ሜትር ርዝመትና 42 ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን፣ ከ41 ሺህ ቶን በላይ ክብደትና 29 ሺህ ኪዩቢክ ሜትር ጭነት የመያዝ ከፍተኛ አቅም እንዳለው ተገልጿል።

ይህ ዘመናዊ መርከብ በሰአት እስከ 12 ሺህ ቶን ጭነት የማራገፍ አስደናቂ ብቃት ያለው በመሆኑ በአለም የመጀመሪያው ፈጣን የመርከብ ስያሜን ተጎናጽፏል።

እንደነዚህ ያሉ የቴክኖሎጂ ምጥቀቶች በዓለም አቀፍ የባህር ላይ ጭነት እና ትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ላይ ከፍተኛ እና አዎንታዊ ለውጥ እንደሚያመጡ ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...