በሞሮኮ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የሰነበተው የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ሌሊት ሰባት ሰአት አካባቢ ተጠናቋል።
ለፍፃሜ የደረሱት ሞሮኮና ናይጄሪያ ያደረጉት ጨዋታ ማራኪ ፉክክርን አስተናግዷል።
ሞሮኮዎች በቺዝላን ቼባክና ፣ በሳና ምሶዴ ሁለት ግቦች 2 ለ 0 ሲመሩ ቆይተው በስተመጨረሻ 3 ለ 2 ተሸንፈዋል።
የናይጄሪያን ሶስት ግቦች ኤስቴር ኦኮሮንኮ ፣ ፎላሻድና ጄኒፈር ኢቼጊኒ አስቆጥረዋል።
ሞሮኮ ለሁለት ተከታታይ ግዜያት ለአፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ ደርሳ ስትሸነፍ ናይጄሪያ ለ10ኛ ግዜ ዋንጫውን አንስታለች።
