አሃዱ ባንክ ከ2.1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማስመዝገብን ያስታወቀ ሲሆን ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ1 ቢሊዮን ብር ጭማሪ ወይም የ90.9 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ገልጿል።
የባንኩ አጠቃላይ ትርፍ የእርጅና ቅናሽ እና ተያያዥ ወጪዎችን ጨምሮ፣ ለመጠባበቂያ ከተቀመጠው እና ከግብር በፊት 569 ሚሊዮን ብር ማትረፉን በሪፖርቱ ተመላክቷል።
ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው ትርፍ በ450 ሚሊዮን ብር ብልጫ ያለው ሲሆን፣ የ278.1 በመቶ እድገት አስመዝግቧል።
የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ 7.8 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው የሒሳብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ68 በመቶ ዕድገት በማሳየቱና በውጭ ምንዛሪ ገቢ ረገድም ከ88 ሚሊዮን ዶላር በላይ መሰብሰብ መቻሉን አስረድተዋል።
የደንበኞች ቁጥር 1.1 ሚሊዮን መድረሱን የገለፀው ባንኩ አጠቃላይ ሀብቱ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ በማድረስ የ57 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን አስታውቋልአስታውቋል።
CapitalNews
