የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋሽንግተን በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንዳትወስድ አስጠንቅቋል።
እንደ ፋራንስ 24 ዘገባ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ፤ “ዋሽንግተን በሁኔታው ላይ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት እንዳትፈጽም ልናስጠነቅቅ እንወዳለን” ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
“ማንኛውም የአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ ሊተነበዩ የማይችሉ አሉታዊ መዘዞችን የሚያስከትል እጅግ አደገኛ እርምጃ ነው'” ሲሉም አክለዋል።
የሩሲያና የቻይና መሪዎች በስልክ ካደረጉት ውይይት በኋላ፤ የክሬምሊን አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ሞስኮ እና ቤጂንግ የግጭቱ ፍጻሜ በፖለቲካዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች ብቻ መፈታት አለበት ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
ባለፈው ሳምንት የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከእስራኤል እና ከኢራን መሪዎች ጋር በስልክ ተነጋግረው ነበር።
