ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

Date:

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው አደገኛ አካሄድ ብዙ ቀውስ እንደሚያስከትል በተከታታይ ሲገለጽ ቆይቷል።

ከዛም ባለፈ ይህ የተሳሳተ አካሄድ በህዝባችን ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ቀውስና አደጋ ግምት ውስጥ በማስገባት አደጋውን በልኩ ተረድቶ ምክክርና መግባባት እንዲደረግበት ተደጋጋሚ ጥሪ ቀርቧል።

ሆኖም “ተመርጫለሁ” ብሎ በቅርቡ ያወጀው አካል ጥሪውን ችላ በማለት ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም በሰራዊት ጥብቅ ጥበቃ ተደርጎለት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የካቢኔ መሰብሰቢያ ኣዳራሽ ውስጥ “የካቢኔ ስብስባ ጀምሬያለሁ” ብሎ በምስል የተደገፈ መረጃ ይፋ አድርጓል።

ይህ ድርጊት የቀጣዩ አደገኛ ምዕራፍ መጀመር ይፋ የሆነበት አጥፊ እንቅስቃሴ ስለሆነ፣ ይህን ህገወጥ ተግባር ተከትሎ በህዝባችን ላይ ለሚደርስ ሁሉን አቀፍ ጥፋትና አደጋ ተጠያቂው ራሱ በጉልበት የአስተዳደሩን ስልጣን ለመያዝ እየሞከረ ያለው አካል መሆኑን ለመግለፅ እፈልጋለሁ።

           ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል)
  የትግራይ ጊዜያዊ  አስተዳደር ፕሬዚዳንት
             ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም
                       መቐለ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...

ከ8 ሺህ በላይ ጥንታዊ የብራና ጽሑፎችን እና ሰነዶችን ወደ ዲጂታል ተቀየሩ

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጽሐፍት አገልግሎት ከተለያዩ ተቋማት፣...