አሜሪካ ከፍልስጤም ድጋፍ ጋር በተያያዘ 300 የውጭ አገር ተማሪዎች ቪዛ ሰረዘች

Date:

ከፍልስጤም ድጋፍ ጋር በተያያዘ 300 የውጭ አገር ተማሪዎች ቪዛ መሰረዙን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ገለጹ።

በዩኒቨርስቲዎች ቅጥር ግቢ ለፍልስጤም የሚደረጉ የድጋፍ ሰልፎችን ለመግታት የትራምፕ አስተዳደር እየወሰዳቸው ካሉ እርምጃዎች አንዱ ነው ተብሏል።

“በዚህ ወቅት ከ300 በላይ ሊሆን ይችላል” ሲሉ ነው በጋያና ጉብኝታቸውን እያደረጉ ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች የተናገሩት።

“ከእነዚህ ቀውሶች አንዱን ባገኘን ቁጥር ፤ በየቀኑ የምናደርገው ነን” ብለዋል።

አስተዳደራቸው ጸረ እስራኤል ነው የሚል ትርክት ከሚያራምድባቸው ዩኒቨርስቲዎች መካከል የምን ያህል ተማሪዎች ቪዛ እንደተሰረዘ ተጠይቀው ነው ይህንን ያሉት።

በቱፍትስ ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት ተማሪ ቱርካዊ ከቀናት በፊት በኢሚግሬሽን ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን ሩቢዮ ይህንን ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብለዋል።

በተማሪዋ ላይ ክስ ስለመቅረቡ እስካሁን የተገለጸ ነገር የለም።

ተማሪዋ ሉዊዚያና በሚገኝ የስደተኞች ማሰሪያ ማዕከል ተወስዳለች።

አንድ የፌደራል ዳኛ በማሳቹስተስ እንድትቆይ ውሳኔ ቢያስተላልፉም ነገር ግን ተማሪዋ በሉዊዚያና እንደምትገኝ የፌደራል መዛግብት ያሳያል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...