ከፍልስጤም ድጋፍ ጋር በተያያዘ 300 የውጭ አገር ተማሪዎች ቪዛ መሰረዙን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ገለጹ።
በዩኒቨርስቲዎች ቅጥር ግቢ ለፍልስጤም የሚደረጉ የድጋፍ ሰልፎችን ለመግታት የትራምፕ አስተዳደር እየወሰዳቸው ካሉ እርምጃዎች አንዱ ነው ተብሏል።
“በዚህ ወቅት ከ300 በላይ ሊሆን ይችላል” ሲሉ ነው በጋያና ጉብኝታቸውን እያደረጉ ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች የተናገሩት።
“ከእነዚህ ቀውሶች አንዱን ባገኘን ቁጥር ፤ በየቀኑ የምናደርገው ነን” ብለዋል።
አስተዳደራቸው ጸረ እስራኤል ነው የሚል ትርክት ከሚያራምድባቸው ዩኒቨርስቲዎች መካከል የምን ያህል ተማሪዎች ቪዛ እንደተሰረዘ ተጠይቀው ነው ይህንን ያሉት።
በቱፍትስ ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት ተማሪ ቱርካዊ ከቀናት በፊት በኢሚግሬሽን ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን ሩቢዮ ይህንን ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብለዋል።
በተማሪዋ ላይ ክስ ስለመቅረቡ እስካሁን የተገለጸ ነገር የለም።
ተማሪዋ ሉዊዚያና በሚገኝ የስደተኞች ማሰሪያ ማዕከል ተወስዳለች።
አንድ የፌደራል ዳኛ በማሳቹስተስ እንድትቆይ ውሳኔ ቢያስተላልፉም ነገር ግን ተማሪዋ በሉዊዚያና እንደምትገኝ የፌደራል መዛግብት ያሳያል።
