“አረጋውያንን እመግባለሁ ጤንነቴን እጠብቃለሁ!” በሚል መሪ ቃል የሜሪጆይ ሩጫ ተካሄደ

Date:

ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ” አረጋውያንን እመግባለሁ ጤንነቴን እጠብቃለሁ በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው 5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ተካሄደ።

መነሻውንና መድረሻውን አዲሱ ፒኮክ መናፈሻ አከባቢ ባደረገው 5ኪሎ ሜትር ሩጫ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በላይ ደጀን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ቆንጅት ደበላ፣ የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራች ሲስተር ዘቢደር ዘውዴን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ ታዋቂ አርቲስቶች፣ የስፖርት ቤተሰቦች፣ ወጣቶች፣ ታዳጊዎች እና የከተማው ነዎሪዎች በስፋት ተሳትፈውበታል።

ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ላለፉት 31 ዓመታት ለተቸገሩ ህጻናት እና አረጋውያን የሰብአዊ ድጋፍ ሲያካሂድ መቆየቱን የገለፁት ሲስተር ዘቢዳር በቀጣይም ይህን ድጋፉን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከተለያዩ ግብረሰናይ ድርጅቶች እና ተቋማት ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...