አራተኛ ቀኑን በያዘው አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነት ዐበይት ክስተቶች

Date:

አራተኛ ቀኑን የያዘው በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥቃት የተጀመረው የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት በርካታ የአካበቢውን አገራት ለኢራን ጥቃት አጋልጦ ቀጥሏል።

  • ዛሬ ማክሰኞ ከማለዳ ጀምሮ እስራኤል በቴህራን እና ቤይሩት “ወታደራዊ ዒላማዎች” ባለቻቸው ስፍራዎች ላይ “ተከታታይ የአየር ጥቃቶች” እየፈጸመች መሆኑን አስታውቃለች።
  • የሳዑዲ መከላከያ ሚኒስቴር በሪያድ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ላይ በሁለት ድሮኖች ጥቃት መፈጸሙን እና መጠነኛ ጉዳት መድረሱን ገልጿል።
  • የኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን በባህሬን በሚገኘው የአሜሪካ አየር ኃይል ማዘዣ እና የሠራተኞች ሕንጻ ላይ ጥቃት መድረሱን ዘግበዋል።
  • የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማርኮ ሩቢዮ የአገሪቱ ጦር በኢራን ላይ የሚፈጽመው “ከባዱ ጥቃት ገና እየመጣ ነው” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
  • ጦርነቱ ከጀመረ ጊዜ አንስቶ ስድስት የአሜሪካ ወታደሮች ተገድለዋል።
  • በኩዌት የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በቀጠናው የተፈጠረን ውጥረት በመጥቀስ ዝግ መሆኑን አስታውቋል።
  • እስራኤል ወደ ሊባኖስ እግረኛ ጦሯን በማስገባት “ተጨማሪ ቁልፍ ስፍራዎችን” ልትቆጣጣር መሆኑን አስታውቃለች።
  • የዩኬው ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኪር ስታርመር መንግሥታቸው ጥቃትን ተከትሎ በኢራን በሚመጣ የመንግሥት ለውጥ እንደማያምን ተናግረዋል። ዶናልድ ትራምፕ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተባባሪ አይደሉም ሲሉ ከስሰዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን...