አራት ሆቴሎች 564 ሚሊዮን ብር ትርፍ አስመዘገቡ

Date:

ሂልተን ሆቴልን ጨምሮ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር የሚተዳደሩ አራት የቱሪዝም ዘርፍ ድርጅቶች፣ በ2017 የበጀት ዓመት ከታክስ በፊት 564.2 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘታቸው ተገለጸ። ይህ ውጤት ከታቀደው የትርፍ ግብ በ37 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ባደረገዉ የስራ አፈጻጸም ግምገማ ፣ የስፓ አገልግሎት ኢንተርፕራይዝ (ፍል ዉሃ)፣ የጊዮን ሆቴሎች ኢንተርፕራይዝ፣ ሂልተን ሆቴል እና የገነት ሆቴልን ያካተተውን የሆቴል ዘርፍ አፈጻጸም ላይ ትኩረት አድርጓል።

ድርጅቶቹ በድምሩ 2.1 ቢሊዮን ብር ገቢ በማሰባሰብ ከታለመው 114 በመቶ ማሳካት ችለዋል የተባለ ሲሆን አሁን ላይ እያደገ የመጣውን የገበያ ፍላጎት እና የቱሪስቶች ፍሰት በመጠቀም ንግዳቸውን እንዲያሰፉ አሳስቧል።

ለዘላቂ እድገት ሲባልም የደንበኞችን እርካታ ማሻሻል፣ ዘመናዊ የግብይት ስልቶችን መጠቀም፣ እንዲሁም ዲጂታል አገልግሎትና የቦታ ማስያዣ ስርዓቶችን ማዘመን እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ተሰጥቷል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...