አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

Date:

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ አርሰናል በኢምሬትስ ቦርንማውዝን ያስተናግዳል፡፡

የሊጉ መሪ አርሰናል በሊጉ አምስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት እና መሪነቱን ለማጠናከር ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ያለፉትን አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ተጋጣሚው ቦርንማውዝ በበኩሉ÷ ወደ ድል ለመመለስ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አርሰናል የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ማንቼስተር ሲቲ እስኪጫወት ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ 12 ከፍ የሚያደርግ ይሆናል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በአንፊልድ ሮድ ፉልሃምን ይገጥማል፡፡

ሊቨርፑል በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ይፋለማል፡፡

ተጋጣሚው ፉልሃም በበኩሉ÷ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት የሚያደርገው ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በርንሌይ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከ ኤቨርተን ሌሎች በሊጉ የሚደረጉ የዛሬ ጨዋታዎች ናቸው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...