በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ አርሰናል በኢምሬትስ ቦርንማውዝን ያስተናግዳል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል በሊጉ አምስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት እና መሪነቱን ለማጠናከር ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ያለፉትን አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ተጋጣሚው ቦርንማውዝ በበኩሉ÷ ወደ ድል ለመመለስ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አርሰናል የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ማንቼስተር ሲቲ እስኪጫወት ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ 12 ከፍ የሚያደርግ ይሆናል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በአንፊልድ ሮድ ፉልሃምን ይገጥማል፡፡
ሊቨርፑል በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ይፋለማል፡፡
ተጋጣሚው ፉልሃም በበኩሉ÷ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት የሚያደርገው ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በርንሌይ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከ ኤቨርተን ሌሎች በሊጉ የሚደረጉ የዛሬ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
