አንዲት እናት 4 ልጆችን በሰላም ተገላገለች

Date:

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን በጋዘር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ዛሬ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ላይ አንዲት እናት 4 ልጆችን በሰላም ተገላግላለች።

አራቱም ሕጻናት በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የጋዘር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ዶ/ር ወንድሜነህ ካሳሁን ለኢቢሲ ዶትስትሪም ገልጸዋል።

ከመውለጃ ጊዜዋ ቀድሞ ምጥ የመጣባት እናት ወ/ሮ ደስታ፣ ለአንድ ሳምንት ያክል በሆስፒታሉ የሕክምና ክትትል ስታደርግ መቆየቷን የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቱ ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለትም በቀዶ ሕክምና ታግዛ መውለዷን ዶ/ር ወንድሜነህ ገልጸው፤ አራቱም ሕጻናት በሆስፒታሉ አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።

አራት ልጆችን በአንድ ጊዜ የተገላገለችው እናት ከዚህ ቀደም ሁለት መንትያ ልጆች መውለዷን አስታውሰው፤ የዛሬውን አይነት ክስተት በሆስፒታሉ ታሪክ አጋጥሞ እንደማያውቅ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቱ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...