ሐጂ ደርባቸው እኔ ሰው ነኝ፤ ደንዲ የግዞት አንባ፤ የአጋደለ ሚዛን፣ ልጅነት ድህነትና ዳኝነት እና ጆፎረ ምዕራፍ 1 የተባሉ መጽሐፎችን ፅፈው ለህትመት ያበቁ ሲሆን ጆፎር ምዕራፍ ሁለትንም እንዲሁም እኒህ ደራሲ እና አንጋፋ የሕግ ሰው ለጉራጌ ብሎም ለሀገራችን የሽምግልና፣ የፍትህ እና በራስ መተማመን ምልክት ናቸው።
የ12 ልጆች አባትና የ33 የልጅ ልጆች ያፈሩት እኚሁ የዕድሜ ባለፀጋ አባት የተወለዱት ጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የፈ በተባለ አነስተኛ መንደር ነበር፡፡
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት እንዲመሰረት በማድረግ ሂደትም የእርሳቸው ሚና ከፍ ያለ እንደነበርም ይጠቀሳል።
የህዳሴ ግድቡ የተገነባበት ቦታ እና ሌሎች የአባይ ተፋሰስ ፕሮጀክቶች ሲጠኑ የቡድኑ ተሳታፊ በመሆን ለአሁኑ ትውልድ ህያው ምስክር ነበሩ።
ሐጂ ደርባቸው መሐመድ ገለቱ በድሜ ዘመናቸው ሁሉ ቅን ለሆነው አገልግሎታቸው እና በጉራግኛ ባህል፣ ቋንቋ እና ስነ ፁሁፍ ጉዞ ውስጥ ላበረከቱ አስተዋጽኦ ይህንን የኬር ሽልማት ተሸላሚ ነበሩ።
ምንጭ፡ ዓለም አቀፍ የጉራጌ ማህበር
