አያቶላህ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን የኢራን መንግሥት አረጋግጦ 40 የሐዘን ቀናት አወጀ

Date:

የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን የኢራን መንግሥት አረጋግጦ 40 የሐዘን ቀናት አወጀ።

መሪው እስራኤል እና አሜሪካ ቅዳሜ ዕለት ቴህራን ውስጥ በፈጸሙት ጥቃት መገደላቸውን የአገሪቱ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን አረጋገጡ።

ከኢራን ብሔራዊ የደኅነንት ጠቅላይ ምክር ቤት ወጥቶ በአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን በተነበበው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው አያቶላህ ኻሜኒ የተገደሉት ቅዳሜ ጠዋት ጽህፈት ቤታቸው ላይ በተፈጸመው ጥቃት ነው።

የጠቅላይ መሪውን ሞት ተከትሎ በመላው አገሪቱ 40 የሐዘን ቀናት የታወጀ ሲሆን፣ የባለሙያዎች እና የሃይማኖት መሪዎች ምክር ቤት የሆነው የአመራር ጉባዔ በአስቸኳይ የተገደሉትን መሪ የሚተካ ሰው ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል።

የአገሪቱ ፕሬዝዳንት እና ሌሎች ሁለት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በቀጣይ የሚደረገውን የመሪ ሽግግር እንደሚመሩ ተገልጿል።

በቅዳሜ ዕለቱ ጥቃት ከአያቶላህ ኻሜኒ በተጨማሪ ከ200 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ቀይ ጨረቃ እና ሌሎችም ምንጮች ያስታወቁ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል 40 የሚሆኑት የኢራን መንግሥት ባለሥልጣናት እንደሆኑ እየተነገረ ነው።

በጥቃቱ የኻሜኒ ሴት ልጅ፣ ባሏ እና የልጅ ልጃቸው መገደላቻውን ከኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ጋር ቅርብት ያላቸው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...