አዲስ ቻምበር ሁለት አዳዲስ ምክትል ዋና ጸሐፊዎች ሾመ

Date:

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) ቦርድ ካለፈው የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ የሚሆን የሁለት ምክትል ዋና ጸሐፊዎች ሹመት ማድረጉን አስታውቋል።

በዚህም መሠረት አቶ ካሣሁን ማሞ የንግድ ልማት እና የአድቮኬሲ ዘርፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ ሆነው ሲሾሙ አቶ ጀማል ሰይድ ደግሞ የአባላት እና ተቋማዊ ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ ሆነው ተሰይመዋል።

አቶ ካሳሁን በምክር ቤቱ ውስጥ ለ11 ዓመታት በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ ሲሆን፣ ማለትም የአድቮኬሲና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር እንዲሁም የውጭ ግንኙነትና ሚዲያ ሥራ አስኪያጅ ሆነው ሰርተዋል።

በተጨማሪም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ውስጥ አንጋፋ የቢዝነስና ኢኮኖሚ ኤዲተር የነበሩ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ6 ዓመታት በከተማና ልማት ኢኮኖሚክስ መምህርነት ማገልገላቸው መረጃዎች ያሳያሉ።

በሌላ በኩል ደግሞ አቶ ጀማል ሰይድ በተለያዩ የግል ተቋማት ውስጥ በዋና ስራ አስፈጻሚነትና በምክትልነት የአመራር ልምድ ያላቸው ሲሆን፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም በዲንነትና በመምህርነት አገልግለዋል።

በ1939 ዓ.ም የተመሠረተው የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት፣ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ቀዳሚና አንጋፋ የንግድ ምክር ቤት መሆኑ ይታወቃል።

ተቋሙ የዓለም ንግድ ምክር ቤቶች ፌዴሬሽን አባል በመሆን የዓለም አቀፍ ትስስር ያለው ሲሆን፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እንዲያድግና እንዲሰፋ የድጋፍና የጥቅም ተሟጋችነት ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ይነገራል።

ቦርዱ በቅርቡ አቶ ዘካርያስ አሰፋን ዋና ጸሐፊ አድርጎ መሾሙ የሚታወስ ሲሆን፣ የአሁኑ የምክትል ዋና ጸሐፊዎች ሹመት የምክር ቤቱን የአመራር አቅም ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...