የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከዛሬ የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የ”አዲስ ስታንዳርድ” የበይነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን የምዝገባ ምስክር ወረቀትን ሰርዟል። ሚዲያው እውቅናውን ተነፍጓል የስራ ፍቃዱን ተነጥቋል።
ባለስልጣኑ ሚዲያው የሀገርንና የሕዝብን ብሔራዊ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ዘገባዎችን በተደጋጋሚ በማሰራጨቱ እና በተሰጠው ምክርና ማስጠንቀቂያ ባለመታረሙ መሆኑን ገልጿል።
የአዲስ ስታንዳርድ ዋና አዘጋጅ ዮናስ ከድር የቀረበውን ክስ ውድቅ አድርገዋል።
” እስካሁን ምንም ዓይነት መደበኛ ማስጠንቀቂያ አልደረሰንም ” በማለት ” ክሱ ከእውነት የራቀ ነው ” ሲሉ ገልጸዋል።
” ‘ አዲስ ስታንዳርድ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎች ደርሰውታል ‘ የሚለው ክስ ከእውነት የራቀ ነው። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ቀደም ሲል ስለነበሩ የሕግ ጥሰቶችም ሆነ ስለተወሰዱ እርምጃዎች ለአዲስ ስታንዳርድ የዜና ክፍል በይፋ ያሳወቀው ነገር የለም ” ብለዋል።
አሳታሚው ጃኬን ፐብሊሺንግ መብቱን ለማስከበር የሕግ አማራጮችን እየተመለከተ መሆኑን አስታውቋል።
