የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ላደረሱት የቦንብ ጥቃት ለመበቀል ለስድስተኛ ጊዜ ጥቃት እየፈፀመ መሆኑን የኢራን መንግስት ሚዲያ ዘግቧል።
በእስራኤል እና በአካባቢው በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ላይ “ሰፋ ያለ ሚሳኤል እና ሰው አልባ አውሮፕላን” ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።
27 የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች፣ እንዲሁም የእስራኤል ቴል ኖፍ አየር ማረፊያ፣ በቴል አቪቭ የሚገኘው የእስራኤል ጦር አዛዥ ዋና ፅህፈት ቤት ሃኪሪያ እና በተመሳሳይ ከተማ በሚገኝ አንድ ትልቅ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ላይ ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ገልጿል።
የኢራን ሃይሎች “የተለየ እና ከባድ የበቀል እርምጃን በተከታታይ” እንደሚተገብሩም አክለዋል።
