ኢራን 150 ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል ተኮሰች

Date:

የአሜሪካ ጦር ወደ እስራኤል የተተኮሱትን የኢራን ሚሳኤሎችን ለመምታት መርዳቱን ሁለት የአሜሪካ ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡

ትናንት በተጀመረውና የኢራንን የተለያዩ ቦታዎች ካጠቃው የእስራኤል ወታደራዊ እርምጃ ተከትሎ ኢራን ማምሻውን በእስራኤል ከተሞች ላይ የሚሳኤል ጥቃት ፈፅማለች፡፡

ኢራን በፈፀመችው ጥቃት እስካሁን 150 የሚሆኑ ባለስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል መተኮሷ ተገልጿል፡፡

በተለያዩ የቴል አቪቭ ቦታዎች ላይ በወደቁት የኢራን ሚሳኤሎች ምክንያት የተነሳውን እሳት ለማጥፋት የእሳት አደጋ ሰራተኞች መሰማራታቸውም ተነግሯል።

በዚህ የኢራን የሚሳኤሎች ጥቃት እስካሁን 40 እስራኤላውያን መጎዳታቸውንና ሁለቱ የከፋ ጉዳት እንዳጋጠማቸው ቲአርቲ ዘግቧል።

የኢራንን ሚሳኤሎች ለማክሸፍ እስራኤል አይረን ዶም ፀረ ሚሳኤሎችን መተኮሷም ነው የተገለፀው፡፡

ከዚህ ጥቃት በኋላ መግለጫ የሰጡት የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ኢዝራኤል ካትዝ፤ ኢራን አሁን ቀይ መስመር አልፋለች፤ ለዚህም የኢራን መንግስት ዋጋ ይከፍላል ብለዋል።

በጥቃቱ ላይ የአሜሪካ ጦር ወደ እስራኤል የተተኮሱትን የኢራን ሚሳኤሎችን ለመምታት እርዳታ መስጡትን ሁለት የአሜሪካ ባለስልጣናት መግለጻቸውን ቢቢሲ በዘገባው አመልክቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...