በቻይና ናንጂንግ እየተካሄደ ባለው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች የ3000 ሜትር ፍጻሜ በአትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አማካኝነት የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች።
ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ብርቄ ኃየሎም አምስተኛ ወጥታለች።
ከቀኑ 8 ሰዓት ከ33 ላይ በሚካሄደው የ3000 ሜትር ወንዶች ፍጻሜ አትሌት በሪሁ አረጋዊ፣ አትሌት ጌትነት ዋለ እና አትሌት ቢኒያም መሐሪ ኢትዮጵያን ወክለው ይወዳደራሉ።
