ኢትዮ ቴሌኮምንና ሳፋሪኮምን ለመደገፍ ተስማምተናል – ዊሊያም ሩቶ

Date:

የኬንያና የኢትዮጵያ መንግሥት ኢትዮ ቴሌኮምንና ሳፋሪኮምን በጋራ ለመደገፍ መስማማታቸውን ለአንድ ቀን ይፋዊ ሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ገልጸዋል።

የአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ፀጥታ እንዲሻሻል ኬንያና ኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የገለጹት ፕሬዚዳንት ሩቶ፤ “ለጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ትስስር፣ ዲጂታል ዕድገትና የጋራ ብልጽግና ባለን የጋራ ርዕይ ላይ ተመስርተን ለቀጣናው መረጋጋት፣ ለንግግርና ለአፍሪካዊ መፍትሔዎች ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠናል” ብለዋል።

በጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን የጠቆሙት ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፤ ሁለቱ መሪዎች ከተነጋገሩባቸው ቁልፍ ጉዳዮች መካከል አንደኛው ኢትዮ ቴሌኮምንና ሳፋሪኮምን በጋራ ለመደገፍ መስማማታቸው መሆኑንም አመልክተዋል።

ሁለቱ ተቋማት በቀጠናዊ ገበያው ውስጥ ያሉትን ስትራቴጀካዊ የጋራ ኢንቨስትመንት ዕድሎች በአግባቡ ለመጠቀም ወሳኝ ፋይዳ ያላቸው መሆኑን የገለጹት ፕሬዚዳንት ሩቶ፤ ኢትዮ ቴሌኮምና ሳፋሪኮም ከኬንያና ከኢትዮጵያ መንግስታት ሙሉ ድጋፍ በሚያገኙባቸው ጉዳዮች ላይ መስማማታቸውን በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...