ኤርዶጋን ተቋርጦ የነበረውን የእህል ስምምነት እንደገና ለማስጀመር ከፑቲን ጋር ለመነጋገር ማቀዳቸውን ገለፁ፡፡
የቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ከሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላዲሚር ፑቲን ጋር በነገው ዕለት የስልክ ውይይት ለማድረግ ማሰባቸውን አስታውቀዋል።
ኤርዶጋን የጥቁር ባሕር የእህል ኮሪደር ስምምነትን እንደገና ለመጀመርና በዩክሬን ያለውን ግጭት ለማስቆም አስቻይ መንገዶችን ለመወያየት አቅደዋል።
በውይይቱ ውጤት ዙሪያ ከአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዲሁም ከዓለም መሪዎች ጋር ለመወያያት እንዳሰቡም አመላክተዋል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል።
