በቤቶች ልማት ዘርፍ ላይ ተሠማርቶ የሚገኘው ኤን.ኤም ሲ ሪል ስቴት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ 1ሺህ አቅመ- ደካሞችና ወላጅ አልባ ለሆኑ ህጻናት የቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።
ድርጅቱ ከዚህ ቀደም፣ 100 ወላጅ አልባ ህፃናትን ሲደግፍ እንደነበር ይታወቃል፡፡
የኤን. ኤም. ሲ ሪል ስቴት ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ መሠረት መኮንን እንደተናገሩት ድርጅታቸው የመረዳዳት እና አንዱ ሌላውን ደግፎ የመኖር ባህል እንዳለው ገልፀው በዘንድሮው የትንሳኤ በዓል አቅመ- ደካሞችና ወላጅ አልባ ህጻናት በአሉን ደስ ብሏቸው እንዲያሳልፉ በማሰብ ነው ድጋፍ ያደረግነው ብለዋል፡፡
ድርጅቱ ቱሉ ዲምቱ በሚገኘው የኤን. ኤም. ሲ የግንባታ ቦታ ላይ የርክክብ ስነስርአቱና የማዕድ ማጋራት መርሀ ግብሩ አከናውነዋል።
አቶ መሰረት ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባቀረበላቸው ጥሪ መሠረት ለአቅመ-ደካሞችና ለድሀ ድሀ ነዋሪዎች የሚያገለግሉ ቤቶች ሰርተው አስረክበው እንደነበር አይዘነጋም፡፡
ከዚህም ባሻገር፣ ድርጅቱ የሸገር ዳቦ ሱቆችን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ-ከተማ በሚገኙ 13ቱም ወረዳዎች እንዲገነባ አድርጓል፡፡
በተጨማሪም በ90 ቀን ሰው ተኮር ፕሮጀክት ባለሀብቶችን በማስተባበር አቶ መሠረት ለሀገር የሚጠቅም በጎ ተግባር ማከናወን መቻላቸውንም ተናግረዋል።
ኤን ኤም ሲ ሪል ስቴት በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን የቤት ችግር ለማቃለል በአቃቂ 11 ነጥብ 5 ቢልዮን ብር በሚገመት ካፒታል የተጀመረው የድርጅቱ የግንባታ ስራ 1ሺህ ቤቶችን ሰርቶ የሚያጠናቅቅ ይሆናል ተብሏል።
ድርጅቱ 45 መኖሪያዎችን ሠርቶ ለቤት ፈላጊዎች እያስተላለፈ ይገኛል ።
ድርጅቱ ለአቅመ ደካሞችን እና ወላጅ አልባ ህጻናት ለመደገፍ ባዘጋጀው ሥነ-ስርአት ላይ የመንግስት ሀላፊዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
ቲክ ቶ
