ኤን.ኤም. ሲ ሪል ስቴት የማዕድ ማጋራት እና 45 መኖሪያዎችን ሠርቶ እያስተላለፈ ይገኛል

Date:

በቤቶች ልማት ዘርፍ ላይ ተሠማርቶ የሚገኘው ኤን.ኤም ሲ ሪል ስቴት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ 1ሺህ አቅመ- ደካሞችና ወላጅ አልባ ለሆኑ ህጻናት የቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

ድርጅቱ ከዚህ ቀደም፣ 100 ወላጅ አልባ ህፃናትን ሲደግፍ እንደነበር ይታወቃል፡፡

የኤን. ኤም. ሲ ሪል ስቴት ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ መሠረት መኮንን እንደተናገሩት ድርጅታቸው የመረዳዳት እና አንዱ ሌላውን ደግፎ የመኖር ባህል እንዳለው ገልፀው በዘንድሮው የትንሳኤ በዓል አቅመ- ደካሞችና ወላጅ አልባ ህጻናት በአሉን ደስ ብሏቸው እንዲያሳልፉ በማሰብ ነው ድጋፍ ያደረግነው ብለዋል፡፡

ድርጅቱ ቱሉ ዲምቱ በሚገኘው የኤን. ኤም. ሲ የግንባታ ቦታ ላይ የርክክብ ስነስርአቱና የማዕድ ማጋራት መርሀ ግብሩ አከናውነዋል።

አቶ መሰረት ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባቀረበላቸው ጥሪ መሠረት ለአቅመ-ደካሞችና ለድሀ ድሀ ነዋሪዎች የሚያገለግሉ ቤቶች ሰርተው አስረክበው እንደነበር አይዘነጋም፡፡

ከዚህም ባሻገር፣ ድርጅቱ የሸገር ዳቦ ሱቆችን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ-ከተማ በሚገኙ 13ቱም ወረዳዎች እንዲገነባ አድርጓል፡፡

በተጨማሪም በ90 ቀን ሰው ተኮር ፕሮጀክት ባለሀብቶችን በማስተባበር አቶ መሠረት ለሀገር የሚጠቅም በጎ ተግባር ማከናወን መቻላቸውንም ተናግረዋል።

ኤን ኤም ሲ ሪል ስቴት በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን የቤት ችግር ለማቃለል በአቃቂ 11 ነጥብ 5 ቢልዮን ብር በሚገመት ካፒታል የተጀመረው የድርጅቱ የግንባታ ስራ 1ሺህ ቤቶችን ሰርቶ የሚያጠናቅቅ ይሆናል ተብሏል።

ድርጅቱ 45 መኖሪያዎችን ሠርቶ ለቤት ፈላጊዎች እያስተላለፈ ይገኛል ።

ድርጅቱ ለአቅመ ደካሞችን እና ወላጅ አልባ ህጻናት ለመደገፍ ባዘጋጀው ሥነ-ስርአት ላይ የመንግስት ሀላፊዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

ቲክ ቶ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...