ኤዜ ሀትሪክ በሰራበት ጨዋታ አርሰናል አሸነፈ

Date:

በ12ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሰሜን ለንደን ደርቢ አርሰናል ቶተንሀም ሆትስፐርን 4 ለ 1 አሸንፏል፡፡


በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ኤቤሬቺ ኤዜ ሦስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል፡፡ ሌአንድሮ ትሮሳርድ ደግሞ አንድ ግብ ያስቆጠረ ተጫዋች ነው፡፡
ከጨዋታው አንድ ቀን በፊት በነበራቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ኤዜ ማነው በማለት ሊቀልዱ የሞከሩት የቶተንሀሙ አሰልጣኝ ቶማስ ፍራንክ እንግሊዛዊው ተጫዋች ሀትሪክ በመስራት በሚገባ መልስ ሰጥቷቸዋል፡፡
በጨዋታው ሪቻርልሰን የቶተንሀምን ብቸኛ ግብ አስገኝቷል፡፡
212ኛውን የሰሜን ለንደን ደርቢ በድል ያጠናቀቁት መድፈኞቹ ከተከታያቸው ቼልሲ ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት በማስፋት ሊጉን በ29 ነጥብ እየመሩ ይገኛሉ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...

ከ8 ሺህ በላይ ጥንታዊ የብራና ጽሑፎችን እና ሰነዶችን ወደ ዲጂታል ተቀየሩ

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጽሐፍት አገልግሎት ከተለያዩ ተቋማት፣...

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...