እስራኤል የኢትዮጵያን የባህር በር የማግኘት ጥረት ሙሉ ለሙሉ ትደግፋለች

Date:

ኢትዮጵያ ለኢኮኖሚዋ፣ ሉአላዊነቷና ደህንነቷ የባህር በር እንደሚያስፈልጋት እስራኤል ታምናለች ያሉት በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭራም ንጉሤ ፤ እስራኤልም ኢትዮጵያ ለምታደርገው ጥረት በዲፕሎማሲና በሰላማዊ መንገድ ከኢትዮጵያ ጎን እንደምትቆም ተናግረዋል፡፡

ሁለቱ ሀገራት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው ያሉት አምባሳደር አቭራም፤ ሁለቱ ሃገራት ጥንታዊና ልዩ የሆነ የብዙ አመታት የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያላቸው መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ በዚህኛው ዘመንም ሁለቱ ሀገራት የሚተባበሩና የሚረዳዱ ናቸው ብለዋል፡፡

“በአለም አቀፍ መድረክም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጭምር እስራኤል ኢትዮጵያን ትደግፋለች፤ ኢትዮጵያም እስራኤልን ትደግፋለች፤ ይህ መደጋገፍ ግን በኢኮኖሚውም በጤናውም በግብርናውም ጭምር ነው” ሲሉ አክለዋል፡፡

የእስራኤል ፓርላማ አባል የሆኑት ዶ/ር ጸጋ ፋንታሁን በተመሳሳይ፤ “ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማግኘት መብቷ የተጠበቀ ነው” ብለዋል፡፡

በእስራኤል የኢትዮጵያ አምባሳደር ተስፋዬ ይታይህ በበኩላቸው፤ “በእስራኤል በኩል ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋን የመቃወም አዝማሚያ አለመኖሩን ገልጸዋል፡፡

“ኢትዮጵያ እንደገና መልሳ ወደ ቀይ ባሕር ጠረፍ ብትመጣ አንደኛ ወዳጅ ሀገር ናት፤ በተጨማሪም እስራኤል ኢትዮጵያን መግቢያ በር አድርጋ ስለምትመለከታት ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንድታግዛት ትፈልጋለች” ብለዋል።

ኢትዮ ኤፍኤም-

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...