ከሰሞኑ እስራኤል ሶስት ጋዜጠኞችና ሶስት የተረድኦ ድረጅት ሰራተኞች መግደሏ የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ

Date:

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ማስተባበርያ ኤጀንሲ (ኦቻ) መረጃ መሰረት ከገባ ዘጠኝ ቀናት ብቻ ባስቆጠረው የኤፕሪል ወር እስራኤል አንድ የኤምኤስኤፍ አባልና ሁለት የፍሊስጤም ቀን ጨረቃ ማህበር ሰራተኞችን መግደሏን ገልፆል።

ይህም ከጥቅምት ሰባቱ ጥቃት ወዲህ እስራኤል በጋዛ ላይ በፈፀመቻቸው የተለያየ መልክ ያላቸው ጥቃቶች የተገደሉት የተራድኦ ድርጅት ሰራተኞች ቁጥር 412 አድርሶታል።

ኦቻ አክሎም ሶስት ፍልስጤማውያን ጋዜጠኞችም ባለፈው አንድ ሳምንት መገደላቸውን ያስታወቀ ሲሆን ኤፕሪል 6ና 7 በካንዮንስ በተፈፀሙ ሁለት ጥቃቶች አንዲት ኢስላም ማክዳድ የተሰኘች እንስት ፍሊስጤማዊ ጋዜጠኛን ጨምሮ ሶስቱ ጋዜጠኞች ተገድለዋል። የጋዜጠኞቹን ህይወት በቀጠፉት ጥቃቶች ሴቶችና ህፃናት የሚገኙባቸው በርካታ ሰላማውያን ሰዎች መገደላቸውም ተዘግቧል።

የነዚህ ሶስት የሚድያ ሰዎች ግድያ ደግሞ በአጠቃላይ በእስራኤል ጥቃት በጋዛ የተገደሉት ጋዜጠኞች ቁጥር 208 አድርሶታል ተብሏል።

በሚሊዮን ሙ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዘመን ባንክ ከ10 ቢሊየን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ አገኝ

ዘመን ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ10.2 ቢሊየን ብር በላይ...

የ8ኛው “ንባብ ለሕይወት!” ዓመታዊ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ጋዜጣዊ መግለጫ

ሐምሌ 20/2018 ዓ.ምበ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት እና ንባብ ለህይወት...

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል አቅርቦት ሥርዓት ወደ ዘመናዊና ዲጂታል...

ኢራን ላይ የተደረገው ጦርነት አሜሪካን እንዳዳከማት ባለስልጣኑ ተናገሩ

የአሜሪካው ኮንግረስ አባል ቶማስ ማሲ፣ የትራምፕ አስተዳደር በኢራን ላይ...