ከፍተኛ መኮንኑ ፣ መሐንዲሱ ፣ ደራሲው ሻለቃ ጳውሎስ ጌታቸው አረፉ!

Date:

የአባታቸውን ብ/ጀ ጌታቸው ናደው የውትድርና ፈለግ በመከተል የውትድርና ህይወትን መረጡ። የቀኃሥ ገነት ጦር ት/ቤት ምሩቅ መኮንን በመሆን የውትድርና ህይወት ሀ ብለው ጀመሩ። የአባታቸው በደርግ በግፍ መገደል ተከትሎ ለ7 አመታት በእስር አሳልፈዋል።

በመቀጠል የቀለም ትምህርት በመግፋት በሲቪል ምህንድስና ተመርቀዋል። በስራቸውም በወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች እና ኤርፖርቶች ላይ አሻራቸውን አኑረዋል።

ከመንግስት ለውጥ በኋላም በዚሁ የሲቪል ምህንድስና ሞያቸው ለረጅም አመት ሠርተዋል። በጡረታ ዘመናቸው እና የመኪና አደጋ ከደረሰባቸው በኋላም 3 መፅሀፍትን ፅፈው ለተደራሲያን አቅርበዋል።

ከጋዜጠኛ ደረጀ ሐይሌ ጋር ATRS TV “በነገራችን ላይ ” በሚል ፕሮግራም በ3 ክፍሎች ተቀንብቦ በቀረበው ቆይታቸው ብዙ መሣጭ ታሪኮችን አጫውተውን ነበር። የተዋቂው ሙዚቃ አቀናባሪ አቤል ጳውሎስ አባት ናቸው።የጀነራሉ ልጅ ፣ ወታደሩ ፣ መሐንዲሱ ፣ ፀኃፊው ሻለቃ ጳውሎስ ጌታቸው ነፍስን ፈጣሪ ይማር።

ለቤተሰብ ፣ ወዳጅ እና ዘመድ እንዲሁም ለባልደረቦቻቸው መፅናናትን ያድል።

Via: አብዮታዊው ሰራዊት ገፅ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...