“ከፑቲን ጋር ሐሙስ በቱርክ ለመገናኘት ዝግጁ ነኝ”  ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ

Date:

Update

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ከሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቱርክ ኢስታንቡል ተገናኝተው ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቱ በኤክስ ገጻቸው ሩስያ ለቀጥታ የሰላም ንግግሮች ያቀረበችውን ሀሳብ በደስታ በመቀበል ነገር ግን ድርድር ከመጀመሩ በፊት የተኩስ አቁም መኖር እንዳለበት አሳስበዋል።

የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቀጥታ ውይይት ለመጀመር ያቀረቡትን ጥሪ በጎ ምልክት መሆኑንም ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠቅሰዋል።

ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ሐሙስ ዕለት በቱርክ ኢስታንቡል ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲንን እጠብቃለሁ ብለዋል።

መላው ዓለም ይህን ለረጅም ጊዜ ሲጠብቀው ቆይቷል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ሆኖም ግን ማንኛውንም ግጭት ለማስቆም የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት የተኩስ አቁም ስምምነት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...