የ 2017 የ ኢትዮጵያ ሴቶች ፕርሚየር ሊግ ውድድር በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን አግኝቷል።
ውድድሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሴቶች ቡድን በአንደኝነት ማጠናቀቁን ማረጋገጡ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሴቶች ቡድን በዛሬው ዕለት ለአምስተኛ ተከታታይ አመት ያሳካውን ዋንጫ በይፋ ተረክቧል።
ቦሌ ክፍለከተማ ሴቶች ቡድን የኢትዮጵያ ሴቶች ፕርሚየር ሊግ የፀባይ ዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ የፊት መስመር ተጨዋች ሴናፍ ዋቁማ በ 22 ግቦች የውድድሩ ኮከብ ግብ አግቢ በመሆን አጠናቃለች።
ሊጉንን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በበላይነት ሲያጠናቅቅ
⏩ ሀዋሳ ከተማ 2️⃣ኛ
⏩ ሲዳማ ቡና 3️⃣ኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቅ ችለዋል።
ከፕርሚየር ሊጉ እነማ ወረዱ ?
በዘንድሮው የውድድር አመት ሀሞበርቾ ዱራሜ እና ቂርቆስ ክፍለከተማ ወደ ከፍተኛ ሊጉ መውረዳቸው ተረጋግጧል።
በሌላ በኩል
- ሸገር ከተማ ሴቶች ቡድን እና
- ይርጋጨፌ ወደ ኢትዮጵያ ሴቶች ፕርሚየር ሊግ ማደጋቸውን አረጋግጠዋል።
@Tikvahethsport
