የኢትዮጵያ ሴቶች ፕርሚየር ሊግ ተጠናቀቀ !

Date:

የ 2017 የ ኢትዮጵያ ሴቶች ፕርሚየር ሊግ ውድድር በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን አግኝቷል።

ውድድሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሴቶች ቡድን በአንደኝነት ማጠናቀቁን ማረጋገጡ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሴቶች ቡድን በዛሬው ዕለት ለአምስተኛ ተከታታይ አመት ያሳካውን ዋንጫ በይፋ ተረክቧል።

ቦሌ ክፍለከተማ ሴቶች ቡድን የኢትዮጵያ ሴቶች ፕርሚየር ሊግ የፀባይ ዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ የፊት መስመር ተጨዋች ሴናፍ ዋቁማ በ 22 ግቦች የውድድሩ ኮከብ ግብ አግቢ በመሆን አጠናቃለች።

ሊጉንን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በበላይነት ሲያጠናቅቅ

⏩ ሀዋሳ ከተማ 2️⃣ኛ
⏩ ሲዳማ ቡና 3️⃣ኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቅ ችለዋል።

ከፕርሚየር ሊጉ እነማ ወረዱ ?

በዘንድሮው የውድድር አመት ሀሞበርቾ ዱራሜ እና ቂርቆስ ክፍለከተማ ወደ ከፍተኛ ሊጉ መውረዳቸው ተረጋግጧል።

በሌላ በኩል

  • ሸገር ከተማ ሴቶች ቡድን እና
  • ይርጋጨፌ ወደ ኢትዮጵያ ሴቶች ፕርሚየር ሊግ ማደጋቸውን አረጋግጠዋል።

@Tikvahethsport    

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...