ከ100 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ነጻ የሕክምና አገልግሎት ሊሰጥ ነው

Date:

በተያዘው ክረምት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ100 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ነጻ ሕክምና አገልግሎት የመስጠት ሥራውን በዛሬው እለት መጀመሩን የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜድካል ኮሌጅ አስታውቋል፡፡

የሜዲካል ኮሌጁ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ ጀማል ሺፋ፤ “የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራ ሁሌም የሚሰራ ቢሆንም በዚህ ዓመት ከሐምሌ 21 እስከ ሐምሌ 27 ቀን 2017 ዓ.ም ባሉት ሰባት ተከታታይ ቀናት ብቻ በሚሰጠው የነጻ ምርመራ 100 ሺሕ ሰዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እቅድ ተይዟል” ብለዋል፡፡

በ2016 ዓ.ም. ተመሳሳይ ወቅት ከ94 ሺሕ ለሚበልጡ ሰዎች የነጻ ሕክምና አገልግሎት እንደተሰጠ አስታውሰው፤ የዘንድሮውን መርሃ-ግብር “በጎ ፈቃደኝነት ለጤናማ ማኅበረሰብ” በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ እንደሚገኝም አብራርተዋል፡፡

ነጻ ምርመራው በተለይ የካንሰር፣ የጎሮሮ፣ የዓይን እና መሰል ትላልቅ የበሽታ አይነቶችን የነጻ ምርመራ እንደሚያደርጉ ከ50 በላይ የሕክምና መሳሪያዎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡

የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ በምርመራ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን ለአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ፣ ደም መለሰገስ፣ እና ሌሎችም የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ መሳተፍን እንደሚጨምር ተነግሯል፡፡

(አሐዱ ሬዲዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...

አሜሪካ እና እስራኤል ደቡብ ሊባኖስን ለአገሪቱ ጦር የማስረከብ ዕቅድ

አሜሪካ ድጋፏን በሰጠችው ዕቅድ መሠረት እስራኤል እና ሊባኖስ፤ የደቡብ...

የመሬት ልማትና አስተዳደር በበጀት ዓመቱ 63 በመቶ ያህሉን ማሳካት አልቻለም

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሊገባደድ በተቃረበው በጀት ዓመት ለመሰብሰብ...