ከዚህ በፊት የተለበሱ ልብሶችን (ቦንዳ) በብዛት የምታስገባዋ አፍሪካዊት ሃገር ናይጄሪያ የነበረች ሲሆን አሁን ይህንን ደረጃ ኬንያ መረከቧን ማሳቹሴትስ ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ አስታውቋል።
እንደ መረጃው ከሆነ ኬንያ በ2023 ብቻ 298 ሚሊየን ዶላር ዋጋ ያላቸውን የተለበሱ ልብሶች ወደ ሃገር ውስጥ አስገብታለች።
ከኬንያ በመቀጠል ጋና፣ ደቡብ አፍሪካና ኡጋንዳ ብዙ የተለበሱ ልብሶችን ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ተቀምጠዋል።
ኬኒያዊያን በዚሁ ላይ የተሰማሩ ወደ 2 ሚሊዮን ነጋዴዎችን ድምጽ ያስተጋባል ያሉትን ማኅበርም አላቸው (Mitumba Consortium Association) በዚህ ማኅበራቸው ፖሊሲዎች እንዲሻሻሉ እና በዘርፉ ያሉ የተሳሳቱ የሚሏቸውን ምልከታዎች ይሞግቱበታል።

በሃገራችን ኢትዮጵያም እነዚህ ልብሶች 53 በመቶ የሚሆነውን የጨርቃ ጨርቅ ገበያ እንደያዙ መዘገቡ ይታወሳል።
የተለበሱ ልብሶች ንግድ ትልቅ ኢኮኖሚ የሚፈጥር እንደሆነ የሚከራከሩ ቢኖሩም በዚያው ልክ የቴክስታይሉን ዘርፍ ያቀጭጨዋል በሚል የሚሞግቱም አሉ።
