ኬንያ የተለበሱ ልብሶችን ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ቀዳሚዋ የአፍሪካ ሃገር ሆነች

Date:

ከዚህ በፊት የተለበሱ ልብሶችን (ቦንዳ) በብዛት የምታስገባዋ አፍሪካዊት ሃገር ናይጄሪያ የነበረች ሲሆን አሁን ይህንን ደረጃ ኬንያ መረከቧን ማሳቹሴትስ ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ አስታውቋል።

እንደ መረጃው ከሆነ ኬንያ በ2023 ብቻ 298 ሚሊየን ዶላር ዋጋ ያላቸውን የተለበሱ ልብሶች ወደ ሃገር ውስጥ አስገብታለች።

ከኬንያ በመቀጠል ጋና፣ ደቡብ አፍሪካና ኡጋንዳ ብዙ የተለበሱ ልብሶችን ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ተቀምጠዋል።

ኬኒያዊያን በዚሁ ላይ የተሰማሩ ወደ 2 ሚሊዮን ነጋዴዎችን ድምጽ ያስተጋባል ያሉትን ማኅበርም አላቸው (Mitumba Consortium Association) በዚህ ማኅበራቸው ፖሊሲዎች እንዲሻሻሉ እና በዘርፉ ያሉ የተሳሳቱ የሚሏቸውን ምልከታዎች ይሞግቱበታል።

በሃገራችን ኢትዮጵያም እነዚህ ልብሶች 53 በመቶ የሚሆነውን የጨርቃ ጨርቅ ገበያ እንደያዙ መዘገቡ ይታወሳል።

የተለበሱ ልብሶች ንግድ ትልቅ ኢኮኖሚ የሚፈጥር እንደሆነ የሚከራከሩ ቢኖሩም በዚያው ልክ የቴክስታይሉን ዘርፍ ያቀጭጨዋል በሚል የሚሞግቱም አሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...