የፍትህ ሚኒስቴር ከጥር 01 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሰራተኞቹ የደመወዝ እና የጥቅማጥቅም ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ።
ይህ ማሻሻያ የፍትህ ስርዓቱን ለማሻሻል እና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ ነው ተብሏል።
በተለይም ለጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ፣ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ፣ ረዳት ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ፣ ምክትል ረዳት ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና ምክትል ረዳት ጠቅላይ ዐቃቤሕግ 35% የደመወዝ ጭማሪ፣ 24,000 ብር የመኖሪያ ቤት አበል እና 11,000 ብር የትራንስፖርት አበል ተደርጓል።
በተጨማሪም ለከፍተኛ ዐቃቤ ህግ እና ዐቃቤ ህግ ደረጃ 1፣ 2 እና 3 የደመወዝ ጭማሪ እና የተለያዩ ጥቅማጥቅሞች ተደርገዋል።
ቅዳሜ ገበያ ከሰራተኞቹ እንደሰማችሁ ዐ/ህጎች በደመወዝ ማነስ ምክንያት በከፍተኛ መጠን እየለቀቁ ነበር። የሰራተኛ ፍልሰቱን ትንሽም ቢሆን ሊያስታግሰው ይችላል። ከነበረው ደመወዝ እና ከፐብሊክ ሰርቪስ ሰራተኞች አንፃር ግን የተሻለ ጭማሪ ነው ብለዋል።
