ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሪዮ ዴ ጄኔሮ የብሪክስ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ስኬታማ ትብብርን ለማስቻል አፀፋዊ መተማመንን የሚያሳድጉ ዓለም አቀፍ ተቋማት መኖራቸው አጣዳፊ እንደሆነ አንስተዋል።
ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የጋራ ደኅንነት እና ሁሉን አካታች ብልጽግና ለማምጣት ይረዳ ዘንድ የውሳኔ አሰጣጥ መዋቅራቸው ምሉዕነት ባለው መልክ የሚሻሻልበትን ሁኔታም አፅንኦት ሰጥተዋል።
“ብሪክስ ከጠንካራ አዲስ ሀሳብ ተነስቶ ለዓለም አቀፍ ለውጥ የሚሠራ ብርቱ ኃይል ወደመሆን ተሸጋግሯል። አዳዲስ አባላት በመጨመራቸውም የጋራ ድምፃችን የበለጠ ይጠናከራል።
የጋራ አላማችን የበለጠ ይጠራል አቅማችንም ይሰፋል” ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡
