የሕዳሴ ግድብን የተመለከተ የሰነድ ማስረጃ ያለው እንዲያቀርብ ተጠየቀ

Date:

የሕዳሴ ግድብን የተመለከተ የምስል፣ የጽሑፍ፣ የቪዲዮና መሰል ሰነዶች ያለው ማንኛውም ግለሰብ፤ ወደ ግድቡ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ የሕዝብ ግንኙነት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ እንዲያቀርብ ተጠይቋል፡፡   

በፕሮጀክቱ የማስተባበሪያ ጽፈት ቤት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ግንኙነት የኮሙኬሽን ኃላፊ አቶ ሰለሞን ዳንኤል ለአሐዱ እንደተናገሩት፤ የሰነድ ማስረጃዎቹ የተፈለጉት የግድቡን ሂደት እና ታሪካዊ ሁነቶችን የሚያሳዩ ማስረጃዎች ለዕይታ ለሚቀረቡበት ሙዚየም እንዲያገለግሉ ነው፡፡

እንደ ግብፅ ያሉ ሀገራት በሕዳሴው ግድብ ላይ የሚያሰራጩትን የሃሰት መረጃ ለመከላከል እንዲህ ዓይነት በማስረጃ ላይ የተመሠረቱ ዶክመንቶችን መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑንም ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡

“ሕዳሴው ግድብ በጠላት ፕሮፓጋንዳ የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ደርሷል” ያሉት ኃላፊው፤ የግድቡ ሙሌት ከ98 በመቶ በላይ መድረሱ ተናግረዋል፡፡

(አሐዱ ሬድዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...