አንዲት እናት 4 ልጆችን በሰላም ተገላገለች

Date:

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን በጋዘር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ዛሬ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ላይ አንዲት እናት 4 ልጆችን በሰላም ተገላግላለች።

አራቱም ሕጻናት በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የጋዘር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ዶ/ር ወንድሜነህ ካሳሁን ለኢቢሲ ዶትስትሪም ገልጸዋል።

ከመውለጃ ጊዜዋ ቀድሞ ምጥ የመጣባት እናት ወ/ሮ ደስታ፣ ለአንድ ሳምንት ያክል በሆስፒታሉ የሕክምና ክትትል ስታደርግ መቆየቷን የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቱ ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለትም በቀዶ ሕክምና ታግዛ መውለዷን ዶ/ር ወንድሜነህ ገልጸው፤ አራቱም ሕጻናት በሆስፒታሉ አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።

አራት ልጆችን በአንድ ጊዜ የተገላገለችው እናት ከዚህ ቀደም ሁለት መንትያ ልጆች መውለዷን አስታውሰው፤ የዛሬውን አይነት ክስተት በሆስፒታሉ ታሪክ አጋጥሞ እንደማያውቅ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቱ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...