የረመዳን የበጎ አድራጎት ተግባራት በሌሎች ወራትም መቀጠል ይኖርባቸዋል

Date:

ህዝበ ሙስሊሙ በረመዳን ወቅት ሲያከናውናቸው የቆዩትን የበጎ አድራጎት ተግባራት በሌሎች ወራትም መቀጠል እንዳለበት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ተናገሩ። 

ሼህ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ 1 ሺህ 446ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓልን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም፥ ለእምነቱ ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 446ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓል አደረሳችሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

የረመዳን ወር በአንድነት፣ በፍቅር፣ በአብሮነት፣ በመተጋገዝና በመደጋገፍ ማለፉን ተናግረዋል።

ሕዝበ ሙስሊሙ የዒድ አል-ፊጥር በዓልን ሲያከብር በጾም ወቅት ሲያደርገው እንደነበረው እርስ በርስ በመደጋገፍና ለተቸገሩ ወገኖች በማካፈል ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ሰላም ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፤ እያንዳንዱ ምዕመን ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የበኩሉን መወጣት እንዳለበት ማመልከታቸውን ተዘግቧል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...