የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ከካርቱም ለቆ መውጣቱን አመነ

Date:

ዳጋሎ ዛሬ በሰጡት መግለጫ “በርግጥም ከካርቱም ለቀን መውጣታችንን አረጋግጣለሁ፤ ነገር ግን በጠንካራ ቁርጠኝነት እንመለሳለን” ብለዋል።

ሔሚቲ በሚል ቅጽል ስማቸው የሚታወቁት ዳጋሎ በቴሌግራም በተሰራጨ የተቀዳ ድምጽ ብሔራዊ ጦሩ ካርቱምን በመቆጣጠሩ የየሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለቆ መውጣቱን አረጋግጠዋል።

ዳጋሎ በዚሁ መግለጫቸው “ባለፉት ጥቂት ቀናት ካርቱምን ለቀን ወደ ኦምድርማን ለመውጣት ተገደናል።

ይህም በአመራሩ የተወሰደ ስልታዊ እና የተቀናጀ ዉሳኔ ነበር” ብለዋል ኃይላቸው የበለጠ ተጠናክሮ እና በሸናፊነት ወደ ካርቱም እንደሚመለስ በማመልከት ።

እንደዚያም ሆኖ ግን የብሄራዊ ጦር ይዞታውን እያጠናከረ ወደ ኦምዱርማን የሚያደርገውን ግስጋሴ ቀጥሎ በማዕከላዊ የከተማዋ ክፍል እየደረሰ እንደሚገኝ  ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።

የብሄራዊ ጦሩ አዛዥ ጄነራል ሃምዳን ዳጋሎ ትናንት ቅዳሜ ባወጡት መግለጫ ከአር ኤስ ኤፍ ጋር የሚደረግ ድርድር እንደማይኖር ግልጽ አድርገዋል።

መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...