ዳጋሎ ዛሬ በሰጡት መግለጫ “በርግጥም ከካርቱም ለቀን መውጣታችንን አረጋግጣለሁ፤ ነገር ግን በጠንካራ ቁርጠኝነት እንመለሳለን” ብለዋል።
ሔሚቲ በሚል ቅጽል ስማቸው የሚታወቁት ዳጋሎ በቴሌግራም በተሰራጨ የተቀዳ ድምጽ ብሔራዊ ጦሩ ካርቱምን በመቆጣጠሩ የየሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለቆ መውጣቱን አረጋግጠዋል።
ዳጋሎ በዚሁ መግለጫቸው “ባለፉት ጥቂት ቀናት ካርቱምን ለቀን ወደ ኦምድርማን ለመውጣት ተገደናል።
ይህም በአመራሩ የተወሰደ ስልታዊ እና የተቀናጀ ዉሳኔ ነበር” ብለዋል ኃይላቸው የበለጠ ተጠናክሮ እና በሸናፊነት ወደ ካርቱም እንደሚመለስ በማመልከት ።
እንደዚያም ሆኖ ግን የብሄራዊ ጦር ይዞታውን እያጠናከረ ወደ ኦምዱርማን የሚያደርገውን ግስጋሴ ቀጥሎ በማዕከላዊ የከተማዋ ክፍል እየደረሰ እንደሚገኝ ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
የብሄራዊ ጦሩ አዛዥ ጄነራል ሃምዳን ዳጋሎ ትናንት ቅዳሜ ባወጡት መግለጫ ከአር ኤስ ኤፍ ጋር የሚደረግ ድርድር እንደማይኖር ግልጽ አድርገዋል።
መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም
