የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ከካርቱም ለቆ መውጣቱን አመነ

Date:

ዳጋሎ ዛሬ በሰጡት መግለጫ “በርግጥም ከካርቱም ለቀን መውጣታችንን አረጋግጣለሁ፤ ነገር ግን በጠንካራ ቁርጠኝነት እንመለሳለን” ብለዋል።

ሔሚቲ በሚል ቅጽል ስማቸው የሚታወቁት ዳጋሎ በቴሌግራም በተሰራጨ የተቀዳ ድምጽ ብሔራዊ ጦሩ ካርቱምን በመቆጣጠሩ የየሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለቆ መውጣቱን አረጋግጠዋል።

ዳጋሎ በዚሁ መግለጫቸው “ባለፉት ጥቂት ቀናት ካርቱምን ለቀን ወደ ኦምድርማን ለመውጣት ተገደናል።

ይህም በአመራሩ የተወሰደ ስልታዊ እና የተቀናጀ ዉሳኔ ነበር” ብለዋል ኃይላቸው የበለጠ ተጠናክሮ እና በሸናፊነት ወደ ካርቱም እንደሚመለስ በማመልከት ።

እንደዚያም ሆኖ ግን የብሄራዊ ጦር ይዞታውን እያጠናከረ ወደ ኦምዱርማን የሚያደርገውን ግስጋሴ ቀጥሎ በማዕከላዊ የከተማዋ ክፍል እየደረሰ እንደሚገኝ  ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።

የብሄራዊ ጦሩ አዛዥ ጄነራል ሃምዳን ዳጋሎ ትናንት ቅዳሜ ባወጡት መግለጫ ከአር ኤስ ኤፍ ጋር የሚደረግ ድርድር እንደማይኖር ግልጽ አድርገዋል።

መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...