የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ከካርቱም ለቆ መውጣቱን አመነ

Date:

ዳጋሎ ዛሬ በሰጡት መግለጫ “በርግጥም ከካርቱም ለቀን መውጣታችንን አረጋግጣለሁ፤ ነገር ግን በጠንካራ ቁርጠኝነት እንመለሳለን” ብለዋል።

ሔሚቲ በሚል ቅጽል ስማቸው የሚታወቁት ዳጋሎ በቴሌግራም በተሰራጨ የተቀዳ ድምጽ ብሔራዊ ጦሩ ካርቱምን በመቆጣጠሩ የየሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለቆ መውጣቱን አረጋግጠዋል።

ዳጋሎ በዚሁ መግለጫቸው “ባለፉት ጥቂት ቀናት ካርቱምን ለቀን ወደ ኦምድርማን ለመውጣት ተገደናል።

ይህም በአመራሩ የተወሰደ ስልታዊ እና የተቀናጀ ዉሳኔ ነበር” ብለዋል ኃይላቸው የበለጠ ተጠናክሮ እና በሸናፊነት ወደ ካርቱም እንደሚመለስ በማመልከት ።

እንደዚያም ሆኖ ግን የብሄራዊ ጦር ይዞታውን እያጠናከረ ወደ ኦምዱርማን የሚያደርገውን ግስጋሴ ቀጥሎ በማዕከላዊ የከተማዋ ክፍል እየደረሰ እንደሚገኝ  ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።

የብሄራዊ ጦሩ አዛዥ ጄነራል ሃምዳን ዳጋሎ ትናንት ቅዳሜ ባወጡት መግለጫ ከአር ኤስ ኤፍ ጋር የሚደረግ ድርድር እንደማይኖር ግልጽ አድርገዋል።

መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...