የዚህ በአል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የሲዳማ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።
የሲዳማ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ወሰንየለህ ስምኦን ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት የፍቼ ጫምባላላ በዓል በውስጡ ያሉ እሴቶች የህብረተሰቡን መወዳጀትን ሁሌም የሚያጠናክር በመሆኑ በዓሉ በሚከበርበት ወቅት ብቻ ሳይሆን ሁሌም መጠበቅና ባህል ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
ፍቼ ጫምባላላ በዓል በኢትዮጵያ ደረጃ ከፌዴራልና ከሁሉም ክልሎች እንዲሁም ከውጪ ሀገራት በርካታ ታዳሚዎች ተገኝተው የሚያከብሩት ታላቅ በዓል መሆኑን አቶ ወሰንየለህ በመግለፅ እነዚህን እንግዶች ታሳቢ ባደረገ መልኩ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉንና ገልፀዋል።በዓሉ ያለምንም ጸጥታ ችግር በሰላም እንዲከበር በተለያዩ ጸጥታ አካላት በኩል አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጋል ።
የበዓሉ አከባበር መጋቢት18 በሀዋሳ ሲዳማ ባህል አዳራሽ እንዲሁም የካቲት 19 ቀን2017 በሶሬሳ ጉዱማሌ በተለያዩ ባህላዊ ዝግጅቶች ከተከበረ በኋላ በቀጣይ ለሁለት ሳምንታት በክልሉ ዞኖችና ወረዳዎች በልዩ ልዩ ደማቅ ዝግጅቶች ይቀጥላል ተብሏል።የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ ፍቼ ጫምባላላ በዓል በዩኔስኮ ከተመዘገበ ዘንድሮ 10ኛ አመቱ መሆኑም ተነግሯል።
