የባንኮች ውህደት ለግል ባንኮች በርካታ ጥቅሞችን ይዞ ይመጣል

Date:

የባንኮች ውህደት ለግል ባንኮች በርካታ ጥቅሞችን ይዞ ይመጣል ሲሉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ገለጹ፡፡

የባንኮች ውህደት በዋናነት የባንኮቹን የፋይናንስ አቅም ለመሳደግ እንደሚረዳ አቶ ዘመዴነህ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል፡፡

የባንኮች ውህደት ሀሳቡ ሲታሰብ ቆየት ማለቱን ያነሱት ባለሙያው፤ የግል ባንኮች በኢትዮጵያ እንዲሰሩ የተፈቀደበት ሁኔታ የ30 አመት ታሪክ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ይህም ከ30 በላይ ባንኮች እንዲቋቋሙ ምክንያት መሆኑን ነው ያነሱት፡፡

አንዳንድ የግል ባንኮች የፋይናስ አቅማቸው ዝቅተኛ መሆኑ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለመደገፍ አቅም እንዲያንሳቸው ማድረጉን ጠቅሰዋል፡፡

በአፍሪካ ትልልቅ ባንኮች ዝርዝር ውስጥ 3 የሀገር ውስጥ ባንኮች መገኘታቸውን አንስተው፤ ነገር ግን ደረጃቸው ዝቅ ያለ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ትላልቅ የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባት እንዳለባቸውና የባንኮች ውህደት ለባንኮች እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል፡፡

ባንኮች ሲዋሀዱ በፋይናንስ አቅምም ሆነ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በአዳዲስ አሰራር እና ኢንቨስተሮችን በመሳብ እንደሚጎለብቱ ተናግረዋል፡፡

ብዙ የግል ባንኮች ስጋት ላይ ቢሆኑም ይህ ውህደት ጥቅሙ ላቅ ያለና ወደፊት ለመቀጠል አስፈላጊ ስለመሆኑም ነው የተናገሩት፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...