የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ የኮንስትራክሽን ግብዓት ልማት አቅርቦት ዴስክ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጠንክር መኩሪያ ከኤፍ ኤም 97.1 ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከውጭ የሚገቡ የኮንትራክሽን ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኮንስትራክሽን ግብዓቶችን 80 በመቶ በሀገር ውስጥ ለመተካት የ10 ዓመት እቅድ አቅዶ እየሰራ እንደሆነም አቶ ጠንክር መኩሪያ ተናግረዋል፡፡ በ2017ዓ.ም እቅድ መሰረት 45 በመቶ የነበረው የሀገር ውስጥ የኮንስትራክሽን ግብዓት ምርት ከ8 በመቶ በላይ አድጎ 53 በመቶ መድረሱንም ጠቅሰዋል፡፡
እንደ አቶ መኩሪያ ገለፃ የሲሚንቶ ምርት ፍላጎትን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በሀገር ውስጥ ምርት መሸፈን የተቻለ ሲሆን ማርብል እና ግራናይትም 70 በመቶው በሀገር ውስጥ እየተመረተ እንደሆነ ጠቁመዋል።
የሌሎች የኮንስትራክሽን ግብዓቶችን አቅርቦት ለማሳደግም በዘላቂነት መስራት እንደሚደባ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ የኮንስትራክሽን ግብዓት ልማት አቅርቦት ዴስክ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጠንክር መኩሪያ ተናግረዋል፡፡
